አብነት ዘኦርቶዶክስ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን መሠረታዊ የግእዝ የጸሎት ክፍል ማለትም የዘወትር ጸሎት ፣ ውዳሴ ማርያም ፣ አንቀጸ ብርሃንና ይዌድስዋ መላእክትን በድምጽና በጽሑፍ ያለ አስተማሪ የሚያስተምር ድንቅ መተግበሪያ ነው ።
የአፕሊኬሽኑ መለያዎች
አፕሊኬሽኑ ምንም ዓይነት የኢንተርኔት ግንኙነት የማይፈልግ ነው ።
የድምጽና የጽሑፍ ቅንብሩ ለመማር ምቹ እንዲሆን ተደርጎ የተሠራ አፕሊኬሽን ነው ።
ድምጹ የሚያነበውን ሐረግ ያቀልማል ። ሐረጎችንም በጽሑፉ ብቻ ወደ ፈለጉት አቅጣጫ (ወደፊትና ወደ ኋላ ) ማስኬድ ያስችላል ።
የድምጽ ፍጥነትን መጨመርና መቀነስ ያስችላል ።
ገጾችን በራሱ ከድምጹ ጋር መቀያየር ይችላል ።
የብቁ መምህራን የድምጽ ቀረጻ ነው የተካተተበት ።
ልጆችን ለማስተማር ምቹ ነው ።