በዛዱል መዓድ የሱና መድረሳ ትምህርት ቤት በተከታታይ ሲቀርብ የነበረው ዚክር እና ዱዓእ የመንፈስ ቀለብ በሚል ርዕስ በ43 ክፍሎች ሲሠጥ የነበረው ትምህርት የተጠናቀቀ መሆኑ ይታወሳል ። አሁን ደግሞ ለዓለም ሙስሊም እህት ወንድሞች እናት አባቶች ቤታቸው ቁጭ ብለው ትምህርቱን ያዳምጡ ዘንድ አንድ ጊዜ አፑን ካወረዱት ኢንተርኔት በማያስፈልግ መልኩ በአፕሌኬሽን ተዘጋጅቷል ።
- ከእናንተ የሚጠበቀው ትምህርቱን አዳምጣችሁ ፣ ላልደረሳቸው ሼር በማድረግ ለወዳጅ ዘምድዎ ማዳረስ ብቻ ነው።
- በተለይ ሐገር ቤት ላሉ ቤተሰቦቻችን በዳታ ለሚቸገሩ ይህ አፕ አንድ ጊዜ ካወረዱት አፑ ዳታ አያስፈልገውም ሼር አድርጉላቸው ።
- በተለያዩ የሱና ኡስታዞች ተቀርተው ያለቁ ኪታቦችን ፣ ተፍሲሮችን ፣ እና ሙሓዶራዎችን በአፕልኬሽን መልክ ማሠራት ፣ ፕለይስቶር ላይ ማስጫን ከፈለጋችሁ በዚህ በስልክ ቁጥር +251912768238 ያናግሩን ።