1. የሰውን ዘር ከጥፋት ማዳን የሚችሉ የወንጌል ሰባኪዎች ሁኑ (ዘፍጥረት 6፡5-22)
2. አሁንም እንኳን ከሐጢያቶቻችሁ መዳን አለባችሁ (ዘፍጥረት 6፡1-4)
3. በእነዚህ የመጨረሻ ቀኖች ለደህንነታችሁ ተዘጋጁ (ዘፍጥረት 6፡5-12)
4. በእግዚአብሄር ጽድቅ በማመን ደህንነት ላይ ደርሰናል (ዘፍጥረት 6፡5-12)
5. እምነታችሁን በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ላይ በማኖር ልባችሁን ጠብቁ (ዘፍጥት 6፡13-14)
6. ኢየሱስ ሐጢያቶቻችሁን በሙሉ የመደምሰሱን እውነታ ታውቃላችሁን? (ዘፍጥረት 6፡14)
7. የእግዚአብሄር ሠራተኞች (ዘፍጥረት 7፡1-24)
8. እየቀረበ ላለው የዓለም ፍጻሜ መዘጋጀት አለባችሁ (ዘፍጥረት 7፡1-24)
9. ወደ ደህንነት የሚወስደን እምነት (ዘፍጥረት 7፡1-13)
10. ዓለምን በእግዚአብሄር ዓይኖች እዩት (ዘፍጥረት 7፡1-12)
11. ወደ መርከቡ ለመግባት ያለ ማመንታት የሐጢያቶችን ስርየት መቀበል አለባችሁ (ዘፍጥረት 7፡1-5)
12. ወደ መርከቡ ውስጥ መግባት አለባችሁ (ዘፍጥረት 7፡1-5)
13. እግዚአብሄር ለእኛ ያለው ዕቅድና ልብ (ዘፍጥረት 8፡20-21)
14. በእምነት ሕይወታችን ውስጥ ስምንት ወቅቶች አሉ (ዘፍጥረት 8፡22)
በአንድ ወቅት በብዙዎች ትልቅ ክብር የተሰጠው አንድ መጋቢ ነበር፡፡ ይህ መጋቢ ለመጀመሪያ ጊዜ በኢየሱስ የመስቀል ላይ ደም ባመነ ጊዜ ባለፉት ሐጢያቶቹ ለጎዳው ለእያንዳንዱ ሰው ካሳ በመስጠት የታወቀ ነበር፡፡ ጠለቅ ባለ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ዕውቀቱና የመፈወስ ሐይሉም እንደዚሁ የታወቀ ነበር፡፡ ነገር ግን እንደ አለመታደል ሆኖ ይህ መጋቢ መጽሐፍ ቅዱስ የተናገረለትን የውሃውንና የመንፈሱን እውነተኛ ወንጌል አላወቀም፡፡ በዚህም እርሱ በእግዚአብሄር ዓይኖች ከንቱ ነው፡፡
ታዲያ በዛሬዎቹ ክርስቲያኖች መካከል ይህ የተምታታ እምነት ያላቸው እነማን ናቸው? እነርሱ የጌታ ደቀ መዛሙርት ከሰበኩት የውሃና የመንፈስ ወንጌል ይልቅ በመስቀሉ ደም ብቻ የሚያምኑ ሰዎች ናቸው፡፡ በእነዚህ ተቋማዊ ክርስቲያኖች የተሰበከው ወንጌል የሚናገረው ኢየሱስ በመስቀል ላይ ስላፈሰሰው ደም ነው፡፡ ይህ ሐሰተኛ ወንጌል በክርስትና ላይ ትልቅ ጉዳት በማምጣት በርካታ ምዕመናኖችን የሥነ ምግባርና የራስ ጽድቅ ተገዥዎች በማድረግና ግብዛዊ የሐይማኖት ተለማማጆች ወደ መሆን ዝቅ አድርጎ ለውጦዋቸዋል፡፡
ዛሬም እንኳን ከእነዚህ ክርስቲያኖች ተብዬዎች ብዙዎች አሉ፡፡ ስለዚህ የዛሬው ክርስትና በትልቅ ግራ መጋባት ተጋርዶዋል፡፡ ጌታ በዚህ ዘመንና ጊዜ እንድንይዘው የሚፈልገው ቃል ይህንን የውሃና የመንፈስ ወንጌል ነው፡፡ እውነተኛውን እምነት የሚይዙት ይህንን የውሃና የመንፈስ ወንጌል የሚያምኑና የሚሰብኩ ብቻ ናቸው፡፡ ለዚህ ምክንያቱ እነዚህ ክርስቲያኖች ሐጢያት አልባ መሆናቸው ብቻ ሳይሆን የሌሎችን ሰዎች ሐጢያቶች የመደምሰስንም ሥራ መሥራት የሚችሉ መሆናቸው ነው፡፡
The New Life Mission
https://www.bjnewlife.org
As a pastor, Rev. Paul C. Jong had long struggled to find the answer to receiving the remission of sins. His search led him to discover, as revealed in the Word of God, the righteousness of Jesus Christ who came by the gospel of the water and the Spirit.
This discovery is what led him to his present ministry. To this very day, Rev. Jong has been dedicating his life to The New Life Mission’s literature ministry, proclaiming the gospel of the water and the Spirit together with his coworkers at The New Life Mission to spread the true gospel throughout the whole world.
His books have been translated and published in over 90 languages, and they are now available and read in over 150 countries. Many of his readers are receiving the remission of sins and the Holy Spirit from God thanks to his books, for these books are founded on the true written Word of God. Along with his coworkers around the world, Rev. Jong gives thanks and glory to God for all this wonderful work. Hallelujah!